ምዕራፍ 124

የዳዊት የመዓርግ መዝሙር።

እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ባይሆን እስራኤል እንዲህ ይበል።
2 እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ባይሆን ሰዎች በእኛ ላይ በተነሡ ጊዜ፥
3 ቍጣቸውን በላያችን በነደደ ጊዜ፥ በዚያን ጊዜ ሕያዋን ሳለን በዋጡን ነበር፤
4 በዚያን ጊዜ ውኃ ባሰጠመን ነበር፥ በነፍሳችንም ላይ ፈሳሽ ባለፈ ነበር፤
5 በዚያን ጊዜ የጐርፍ ውኃ በነፍሳችን ላይ ባለፈ ነበር።
6 ለጥርሳቸው ንክሻ ያላደረገን እግዚአብሔር ይባረክ።
7 ነፍሳችን እንደ ወፍ ከአዳኞች ወጥመድ አመለጠች። ወጥመድ ተሰበረ እኛም አመለጥን።
8 ረድኤታችን ሰማይንና ምድርን በሠራ በእግዚአብሔር ስም ነው።