ምዕራፍ 105

ሃሌ ሉያ።

እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ጥሩ፥ ለአሕዛብም ሥራውን አውሩ።
2 ተቀኙለት፥ ዘምሩለት፥ ተአምራቱንም ሁሉ ተናገሩ።
3 በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው።
4 እግዚአብሔርን ፈልጉት ትጸናላችሁም፤ ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ።
5
6 ባሪያዎቹ የአብርሃም ዘር፥ ለእርሱም የተመረጣችሁ የያዕቆብ ልጆች ሆይ፥ የሠራትን ድንቅ አስቡ፥ ተአምራቱን የአፉንም ፍርድ።
7 እርሱ እግዚአብሔር አምላካችን ነው፤ ፍርዱ በምድር ሁሉ ነው።
8 ቃል ኪዳኑን ለዘላለም፥ እስከ ሺህ ትውልድ ያዘዘውን ቃሉን አሰበ፥
9 ለአብርሃም ያደረገውን፥ ለይስሐቅም የማለውን፤
10 ለያዕቆብ ሥርዓት እንዲሆን ለእስራኤልም የዘላለም ኪዳን እንዲሆን አጸና።
11 እንዲህም አለ። ለአንተ የከነዓንን ምድር የርስታችሁን ገመድ እሰጣለሁ፤
12 ይህም የሆነው እነርሱ በቍጥር ጥቂቶች ሰዎች፥ እጅግ ጥቂቶችና ስደተኞች ሲሆኑ ነው።
13 ከሕዝብ ወደ ሕዝብ፥ ከመንግሥታትም ወደ ሌላ ሕዝብ አለፉ።
14 -
15 የቀባኋቸውን አትዳስሱ፥ በነቢያቴም ክፉ አታድርጉ ብሎ፥ ሰው ግፍ ያደርግባቸው ዘንድ አልፈቀደም፥ ስለ እነርሱም ነገሥታትን ገሠጸ።
16 በምድር ላይ ራብን ጠራ፥ የእህልን ኃይል ሁሉ ሰበረ።
17 በፊታቸው ሰውን ላከ፤ ዮሴፍ ለባርነት ተሸጠ።
18 እግሮቹም በእግር ብረት ደከሙ፥ እርሱም በብረት ውስጥ ገባ።
19 ቃሉ እስኪመጣለት ድረስ፥ የእግዚአብሔር ቃል ፈተነው።
20 ንጉሥ ላከ ፈታውም፥ የአሕዛብም አለቃ አስፈታው።
21 የቤቱ ጌታ፥ የጥሪቱ ሁሉ ገዢ አደረገው፥
22 አለቆቹን እንደ ፈቃዱ ይገሥጽ ዘንድ፥ ሽማግሌዎቹንም ጥበበኞች ያደርጋቸው ዘንድ።
23 እስራኤልም ወደ ግብጽ ገባ፥ ያዕቆብም በካም አገር ተቀመጠ።
24 ሕዝቡንም እጅግ አበዛ፥ ከጠላቶቻቸውም ይልቅ አበረታቸው።
25 ሕዝቡን ይጠሉ ዘንድ በባሪያዎቹም ላይ ይተነኰሉ ዘንድ ልባቸውን ለወጠ።
26 ባሪያውን ሙሴን የመረጠውንም አሮንን ላከ።
27 የተኣምራቱን ነገር በላያቸው ድንቁንም በካም አገር አደረገ።
28 ጨለማን ላከ ጨለመባቸውም፤ በቃሉም ዐመፁ።
29 ውኃቸውን ወደ ደም ለወጠ፥ ዓሦቻቸውንም ገደለ።
30 ምድራቸው የንጉሦቻቸውም ቤቶች በጓጕንቸር ሞሉ።
31 ተናገረ፥ የውሻ ዝንብ ትንኝም በዳርቻቸው መጡ።
32 ዝናባቸውን በረዶ አደረገው፥ እሳትም በምድራቸው ተቃጠለች።
33 ወይናቸውንና በለሳቸውን መታ፥ የአገራቸውንም ዛፍ ሁሉ ሰበረ።
34 ተናገረ፥ አንበጣም ስፍር ቍጥር የሌለውም ኩብኩባ መጣ፥
35 የአገራቸውንም ለምለም ሁሉ በላ፥ የምድራቸውንም ፍሬ በላ።
36 የአገራቸውንም በኵር ሁሉ፥ የጕልበታቸውን መጀመሪያ ሁሉ መታ።
37 ከወርቅና ከብርም ጋር አወጣቸው፥ በወገናቸውም ውስጥ ደዌ አልነበረም።
38 ፈርተዋቸው ነበርና ግብጽ በመውጣታቸው ደስ አላት።
39 ደመናን ለመሸፈኛ ዘረጋባቸው፥ እሳትንም በሌሊት ያበራላቸው ዘንድ ዘረጋ።
40 ለመኑ፥ ድርጭትንም አመጣላቸው፥ የሰማይንም እንጀራ አጠገባቸው።
41 ዓለቱን ሰነጠቀ፥ ውኃውም ፈሰሰ፤ ወንዞች በበረሃ ሄዱ፤
42 ለባሪያው ለአብርሃም የነገረውን ቅዱስ ቃሉን አስቦአልና።
43 ሕዝቡንም በደስታ የተመረጡትንም በእልልታ አወጣ።
44 የአሕዛብንም አገሮች ሰጣቸው፥ የወገኖችንም ድካም ወረሱ፥
45 ሕጉን ይጠብቁ ዘንድ፥ ሥርዓቱንም ይፈልጉ ዘንድ። ሃሌ ሉያ