ቃል

0:00
0:00

  • አንተ እንዳልበድል፥ ቃልህን በልቤ ሰወርሁ።
    መዝሙረ ዳዊት 119:11
  • የቃልህ ፍቺ ያበራል፥ ሕፃናትንም አስተዋዮች ያደርጋል።
    መዝሙረ ዳዊት 119:130
  • እርሱም መልሶ። ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው።
    የማቴዎስ ወንጌል 4:4
  • ሰማይና ምድር ያልፋሉ፥ ቃሌ ግን አያልፍም።
    የማቴዎስ ወንጌል 24:35
  • በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። ...ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።
    የዮሐንስ ወንጌል 1:1,14
  • ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ነው፤ ሥጋ ምንም አይጠቅምም፤ እኔ የነገርኋችሁ ቃል መንፈስ ነው ሕይወትም ነው።
    የዮሐንስ ወንጌል 6:63
  • እናንተ ስለ ነገርኋችሁ ቃል አሁን ንጹሐን ናችሁ፤
    የዮሐንስ ወንጌል 15:3
  • የእውነትን ቃል በቅንነት የሚናገር የማያሳፍርም ሠራተኛ ሆነህ፥ የተፈተነውን ራስህን ለእግዚአብሔር ልታቀርብ ትጋ።
    2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2:15
  • የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤
    ወደ ዕብራውያን 4:12
  • ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።
    1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2:3